ዜና ፌ.ቤ.ኮ
Back
የቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች የዲጂታል የአሰራር ሥርዓት ዝርጋታ ላይ የበለጠ ትኩረት አድርገው እየሰሩ ነው

የቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ኮርፖሬሽኑ እያካሄደ ያለውን የዲጅታል የአሰራር ሥርዓት ዝርጋታ የበለጠ ውጤታማ የሚያደርግ እንቅስቃሴ በማከናወን ላይ ናቸው፡፡
ለዓብነትም የቅርንጫፍ ሁለት ጽ/ቤት ባራሱ ባለሙያ በሥራ ላይ ካለው ሶፍትዌር በተጨማሪ ዘመናዊ የቤት አስተዳደር ሶፍትዌር አልምቶ የሲስተሙን ሙከራ ውጤታማነት በቤት አስተዳደር ዘርፍ አመራሮች እንዲገመገም ተደርጓል፡፡
በቅርንጫፍ ሁለት ባለሙያ የለማው ይህ መተግበሪያ በዋናነት ለቤት አስተዳደር ሥራው ተጨማሪ የቴክሎጂ አማራጭ መሆን የሚችል ሲሆን ወደ ሥራ ለማስገባትም በሙከራ ሒደት ላይ ይገኛል፡፡
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን አሰራሩን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታላይዝ የአሰራር ሥርዓት እየቀየረ ሲሆን በማዕከል በአይሲቲ ዳይሬክቶሬት እየለሙ ካሉት በርካታ መተግባሪያዎች በተጨማሪ የቅርንጫፍ ሁለት ጽ/ቤት በራሱ ዓቅም ያለማው መተግበሪያም ለዲጂታላይዜሽን ሒደቱ ተጨማሪ ግብዓት የሚሆን ነው፡፡