ዜና ፌ.ቤ.ኮ ዜና ፌ.ቤ.ኮ

Back

ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ ሚኒስትር እና የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ በጋራ የመስክ ሥራ ጉብኝት አካሄዱ

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ኃለፊ ሚኒስትር እና የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት ክብርት ወ/ሮ አለምጽሐይ ጳውሎስ ከፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር አቶ ረሻድ ከማል ጋር በጋራ በዛሬው እለት የኮርፖሬሽኑ ውጤታማ የሥራ እንቅስቃሴን በመስክ ሥራ ጉብኝት ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡

የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር አቶ ረሻድ ከማል የተቋሙን የሥራ እንቅስቃሴን ጨምሮ ኮርፖሬሽኑ በአጭር ጊዜ ግንባታዎችን ማጠናነቀቅ ስለቻለበት የፕሮጀክት አስተዳደር ሥርዓቱን በተመለከተም ለክብርት ሚኒስትሯ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

ከብርት ሚኒስትሯ በዋናው መ/ቤት እና በቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ዘመናዊ ቴክኖሎጂን መስረት አድርጎ ኮርፖሬሽኑ እያቀረበ ያለውን አገልግሎትና የዲጂታላይዜሽን አሰራር ሥርዓት ዝርጋታ ያለበት ደረጃንም ተመልክተዋል፡፡

በተመሳሳይ ኮርፖሬሽኑ በአጭር ግዜ ገንብቶ ለአገልግሎት ያበቃቸውን ዘመናዊ ሚክስድ አፓርትምንት ሕንጻዎችን የተመለከቱ ሲሆን የኮርፖሬሽኑ ለውጥና የተቋም ግንባታ ያለበት ደረጃ በጣም ጥሩ እንደሆነ ከብርት ሚኒስትሯ የጠቆሙ ሲሆን የኮርፖሬሽኑ አመራርና ሠራተኛ በተገኘው ስኬት ሳይዘናጋ ለላቀ ለውጥና ውጤት እንዲተጋም አበረታተዋል ፡፡

በጉብኝቱ የኮርፖሬሽኑ የማኔጅመንት አበላትም ተሳታፊ ሆነዋል፡፡


ዜና ፌ.ቤ.ኮ ዜና ፌ.ቤ.ኮ

በኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አሰፈፃሚ ክቡር አቶ ረሻድ ከማል የተመራ የልዑካን ቡድን በእንግሊዝ ለንደን የስራ ጉብኝት አካሄደ

በኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አሰፈፃሚ ክቡር አቶ ረሻድ ከማል የተመራ የልዑካን ቡድን በእንግሊዝ ለንደን የስራ ጉብኝት አካሄደ

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በ2015 በጀት ዓመት ገቢውን ለማሳደግ ያከናወናቸው ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆሊዲንግ አስታወቀ

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በ2015 በጀት ዓመት ገቢውን ለማሳደግ ያከናወናቸው ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆሊዲንግ አስታወቀ

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን አመራሮችና ሠራተኞች ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ለአምስተኛ ጊዜ ደም ለገሱ

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን አመራሮችና ሠራተኞች ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ለአምስተኛ ጊዜ ደም ለገሱ

የፌ.ቤ.ኮ ሜይል የፌ.ቤ.ኮ ሜይል

ይከተሉን ይከተሉን

ተዛማጅ ገጾች ተዛማጅ ገጾች