ዜና ፌ.ቤ.ኮ ዜና ፌ.ቤ.ኮ

Back

የአዘርባጃን የቤት ልማት ኤጂንሲ እና የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በቤት ልማት ዙሪያ በጋራ ለመስራት በሚያስችላቸው ጉዳዮች ላይ ስምምነት ደረሱ

በክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የተመራው እና የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ክቡር አቶ ረሻድ ከማልን ያካተተው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የልዑካን ቡድን በቤት ልማት ዙሪያ ባካሄደው ምክክር የአዘርባጃን የቤት ልማት ኤጂንሲ እና የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በጋራ ለመስራት በአዘርባጃን ዋና ከተማ ባኩ ስምምነት ላይ ደርሰዋል ፡፡

የልዑካን ቡድኑ አባል የሆኑት ፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር አቶ ረሻድ ከማል አቻ ከሆነው ተቋም ከአዘርባጃን የቤት ልማት ኤጂንሲ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር ሰፊ ምክክርና ውይይት አድርገዋል፡፡

የአዘርባጃን የቤት ልማት ኤጂንሲ በመንግስት መነሻ የኢንቨስትመንት ፋይናንስ ድጋፍ ተደርጎለት የሚገነባቸውን ቤቶች ከ 30 በመቶ እስከ 40 በመቶ ከገበያው የዋጋ ቅናሽ ያላቸውን ቤቶች ለአገሪቱ ዜጎች በሽያጭ እያቀረበ ገበያ የማረጋጋት ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝም ተጠቅሷል፡፡

የአዘርባጃን የቤት ልማት ኤጂንሲ ከመንግስት የሚያገኘውን መነሻ የኢንቨስትመንት ፋይናንስ ድጋፍ ሙሉ በሙሉ ገበያ ለመረጋጋት ለሚገነባቸው ቤቶች ግንባታ የሚያውል ሲሆን ያገኘውን የበጀት ድጋፍ ለመንግስት የመመለስ ግዴታ የሌለበት ተቋም እንደሆነም ተጠቁሟል፡፡

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሪል ስቴት ገበያውን ለማረጋጋት እያደረገ ላለው ጥረት የአዘርባጃን የቤት ልማት ኤጂንሲ ያለውን ሰፊ ልምድ ለፌዴራል ቤቶች የሚያጋራ ይሆናል፡፡

ሁለቱ ተቋማት በቤት ልማት ዙሪያ በትብብር ለመስራት በሚያስችላቸውን ጉዳዮች ላይ ስምምነት በመደረሱ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የአዘርባጃን የቤት ልማት ኤጂንሲን ልምድና ተሞክሮ በኢትዮጵያ ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰራም ታውቋል፡፡

የቀድሞው ኪራይ ቤቶች የአሁኑ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ራሱን ጠንካራ መንግስታዊ የሪል ስቴት ካምፓኒ ለመሆን በሚያስችለው አግባብ እየደረጀ ሲሆን የሪል ስቴት ገበያው እንዲረጋጋ የራሱን ሚና እየተጫወተ ነው።


ዜና ፌ.ቤ.ኮ ዜና ፌ.ቤ.ኮ

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ቅርንጫፍ ሦስት አዲስ የገነባውን ፅ/ቤት አስመርቋል

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ቅርንጫፍ ሦስት አዲስ የገነባውን ፅ/ቤት አስመርቋል

በኢትዮጵያ የጣሊያን አምባሳደር ክቡር አጉስቶ ፓሊሳ በፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እና ዋንኮ ኢታሊ ጋር በመተባበር እየተከናወነ ያለውን የዘመናዊ ፕሪፋብ ሆም ፋብሪካ ተካላ ቅድመ ዝግጅት ሥራ ጎበኙ

በኢትዮጵያ የጣሊያን አምባሳደር ክቡር አጉስቶ ፓሊሳ በፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እና ዋንኮ ኢታሊ ጋር በመተባበር እየተከናወነ ያለውን የዘመናዊ ፕሪፋብ ሆም ፋብሪካ ተካላ ቅድመ ዝግጅት ሥራ ጎበኙ

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሕንጻን ለማዘመንና ለማስዋብ ስምምነት ፈፀመ

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሕንጻን ለማዘመንና ለማስዋብ ስምምነት ፈፀመ

የፌ.ቤ.ኮ ሜይል የፌ.ቤ.ኮ ሜይል

ይከተሉን ይከተሉን

ተዛማጅ ገጾች ተዛማጅ ገጾች