ግቦች ግቦች

የኮርፖሬሽኑ ዓላማዎች

የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽንን ለማቋቋም በወጣው የሚኒስትሮች ም/ቤት ደንብ ቁጥር398/2009 አንቀፅ 5 መሰረት ኮርፖሬሽኑ የተቋቋመባቸው ዓላማዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡

  1. ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ ቤቶችን የመገንባት፣ የማስገንባት፣ የማከራየት፣ የመሸጥ እንዲሁም የመግዛት፣
  2. የፌደራል መንግስትበባለቤትነት የያዛቸውንቤቶችና ይዞታዎችየማስተዳደር፣የማከራየት፣
  3. ለፌደራል መንግሥት ቤቶችና ህንፃዎች አስፈላጊውን ጥገናና ዕደሳት በማድረግ የመጠበቅና የመንከባከብ፣
  4. የፌደራል መንግሥት ንብረት የሆኑት ቤቶችና ይዞታዎችበሕግ አግባብ መመዝገባቸውንና መጠበቃቸውን የማረጋገጥ፣
  5. የፌደራል መንግሥት ቤቶችን በአግባቡ ለማስተዳደር የሚያስችል ዘመናዊ የቤት አስተዳደር ሥርዓትን በመዘርጋት ሥራ ላይ የማዋል፣
  6. በመንግስት ቤቶችና ይዞታዎች ላይ የሚፈፀሙ ህገ ወጥ ድርጊቶችንየመከላከል፣ የመንግስትን ጥቅምየማስከበር እና አስፈላጊ ህጋዊእርምጃዎችን የመውሰድ፣
  7. መንግስት በሚሰጠው አቅጣጫ መሰረት በመንግስት ወጪ ተሸፍነው ለመንግስት ኃላፊዎች እና ሰራተኞች የመኖሪያ ቤት የመገንባት፣ የማከራየት እና የማስተዳደር፣
  8. ለሚያስተዳድራቸው ቤቶችና ይዞታዎችየቤት ኪራይ ተመን ጥናትየማካሄድና ተግባራዊየማድረግ፣
  9. በሽያጭ እንዲተላለፉበመንግሥት ውሣኔ ውሳኔ የተሰጠባቸውን ቤቶች ዋጋ አተማመን ጥናት የማካሄድ፣ ሲወሰን በውሳኔው መሠረትየመፈፀምናየሽያጭ ገቢየመሰብሰብ፣
  10. ለአስተዳደር አመቺ ያልሆኑ፤ መልሶ ለማልማት የማያስችሉና ኪራያቸው አነስተኛ የሆኑ ቤቶችንና ይዞታዎችን በመንግስት ውሳኔየማስተላለፍ፣
  11. ለተወረሱ ቤቶች የቀድሞ ባለንብረቶች በሕጉ መሠረት አበልየመክፈል፣
  12. ከቤት አስተዳደርና ልማት ጋር የተያያዙ ጥናቶችንበማካሄድበመንግስት ሲፈቀድተግባራዊየማድረግ፣
  13. ከተቆጣጣሪው ባለስልጣን በሚሰጠው አቅጣጫ ላይ በመመስረት በሀገር ውስጥ ተወዳዳሪና አትራፊ ሆኖ እንዲንቀሳቀስ እገዛ የሚያደርጉለትን የሰው ሀይል፣ የፋይናንስና የዘመናዊ አስተዳደር ግብዓቶችን ለማግኘት የሚያስችለውን ጥናት በማካሄድ ተግባራዊየማድረግ፣
  14. ዓላማውን ከግብ ለማድረስ የሚረዱ ሌሎች ተዛማጅ ሥራዎችን የማካሄድዓላማዎች ተሰጥቶታል፡፡

ዜና ፌ.ቤ.ኮ ዜና ፌ.ቤ.ኮ

በኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አሰፈፃሚ ክቡር አቶ ረሻድ ከማል የተመራ የልዑካን ቡድን በእንግሊዝ ለንደን የስራ ጉብኝት አካሄደ

በኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አሰፈፃሚ ክቡር አቶ ረሻድ ከማል የተመራ የልዑካን ቡድን በእንግሊዝ ለንደን የስራ ጉብኝት አካሄደ

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በ2015 በጀት ዓመት ገቢውን ለማሳደግ ያከናወናቸው ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆሊዲንግ አስታወቀ

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በ2015 በጀት ዓመት ገቢውን ለማሳደግ ያከናወናቸው ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆሊዲንግ አስታወቀ

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን አመራሮችና ሠራተኞች ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ለአምስተኛ ጊዜ ደም ለገሱ

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን አመራሮችና ሠራተኞች ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ለአምስተኛ ጊዜ ደም ለገሱ

ኮርፖሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት የሱማሌ ተራ ሳይትን የግንባታ ሒደት ጎበኙ

ኮርፖሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት የሱማሌ ተራ ሳይትን የግንባታ ሒደት ጎበኙ

ኮርፖሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት የሱማሌ ተራ ሳይትን የግንባታ ሒደት ጎበኙ

ኮርፖሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት የሱማሌ ተራ ሳይትን የግንባታ ሒደት ጎበኙ

የፌ.ቤ.ኮ ኢ-ሜይል የፌ.ቤ.ኮ ኢ-ሜይል

ይከተሉን ይከተሉን

ተዛማጅ ገጾች ተዛማጅ ገጾች